Saturday 25 February 2012

የዐብይ ጾም ስብከት (ክፍል 2) በአያሌው ዘኢየሱስ


የዐብይ ጾም ስብከት (ክፍል 2)

የካቲት 15/2004 ዓ.ም.
በአያሌው ዘኢየሱስ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤አሜን፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጾም በድንገት የተገኘ የሰዎች ፍልስፍና ሳይሆን አምላካዊ ሥርዓት ነው፡፡ ጾም መጾም የተጀመረበት ጊዜ ሰው ከተፈጠረበት ጊዜ ጋር የማይተናነስ መሆኑን የምናውቀው እግዚአብሔር አምላክ የቀደሙ ወላጆቻችንን፡- ከዚህ ብሉ፤ ከዚህ ግን አትብሉ (ዘፍ 2፥16-17) በማለት ከደነገገላቸው ትእዛዝ ጋር የሚዛመድ በመሆኑ ነው፡፡ «አትብሉ» ማለት ከተወሰነ ወይም ከተወሰኑ መባልእት «ተከልከሉ» አልፎ ተርፎም «አትንኩት» ማለት ነው፡፡ ዲያብሎስ እናታችን ሔዋንን «በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዟአልን?» (ዘፍ 3፥1) በማለት በጠየቃት ጊዜ እግዚአብሔር ለእርሷና ለባሏ የሰጣቸውን ቀጥተኛ ትእዛዝ ግልጽ በሆነ መንገድ የነገረችው እንዲህ በማለት ነበር፡- «እግዚአብሔር አለ፡- እንዳትሞቱ ከእርሱ አትብሉ፤አትንኩትም፡፡» ዘፍ 3፥3፡፡ እግዚአብሔር አምላክ የአዳምንና የሔዋንን ሕልውና ወይም መኖርና አለመኖርን የወሰነው በመብላትና ባለመብላት ውስጥ ነበር፡፡ አዳምና ሔዋን መብላትን ችለው አለመብላትን ስላልቻሉ ነው ከገነት ተባርረው የሞት ሞት  የተፈረደባቸው፡፡

Friday 24 February 2012

ኪዳነ ምሕረት


ኪዳነ ምሕረት


የካቲት 15/2004 ዓ.ም.
በገብረ እግዚአብሔር ኪደ
Kidane meherete
ኪዳን ማለት በሁለት ወይም ከሁለት በላይ በሆኑ ወገኖች መካከል የሚደረግ ስምምነት፣ ውል ማለት ነው፡፡ ውል “ውል” የሚያሰኘው በውሉ ወይም በስምምነቱ ውስጥ ያሉት ወገኖች እያንዳንዳቸው የሚጠበቅባቸውንና ሊያደርጉት የሚገባቸውን ተግባር ሲኖር ነው፡፡ የሚፈርሰው እንኳ ሁሉም ወገኖች ሲስማሙ ብቻ ነው፡፡ አንዱ ወገን ብቻ ቢያፈርስ ግን እርሱ ውል አፍራሽ ይባላል፡፡ ሓላፊነቱንም እርሱ ይወስዳል፡፡

Tuesday 21 February 2012

ለምን እንጾማለን?

የዐቢይ ጾም ስብከት (ክፍል 1) በአያሌው ዘኢየሱስ


የዐቢይ ጾም ስብከት (ክፍል 1)



የካቲት 13/2004 ዓ.ም
በአያሌው ዘኢየሱስ

ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት በሆነችው በቅድስቲቱ ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ጾም እንደ እንግዳ ደራሽ፤እንደ ወንዝም ፈሳሽ በድንገት የተጀመረ ሥርዓተ አይደለም፡፡ በተለይም በአዲስ ኪዳን ዘመን ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይሆን መድኀኒታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ የመጀመሪያ አድርጎ የሠራው ሕግ ነው፡፡