Wednesday 25 July 2012

"ደጉ መልአክ ገብርኤል" zemari tewodros yosef

ቁልቢ ገብርኤል



ቁልቢ ገብርኤል



ዲያቆን መልአኩ እዘዘው

 ከአዲስ አበባ በስተምሥራቅ 461/ርቀት ላይ በምዕራብ ሐረርጌሀበገረ ስብከት
 ጋራ ሙለታ የሚገኝ ቤተክርስቲያን ነው፡፡ የዚህን ደብርአመሠራረት በተመለከተ 
በብዙ ሊቃውንትየሚተረከው የሚከተለው ነው::በዘጠነኛው //ዮዲት ጉዲት
ተነሥታ አብያተ ክርስቲያናትንስትመዘብር፣ ክርስቲያኖችን ስትገድልና
መጻሕፍትን ስትቆነጻጽል ንጉሥ አንበሣ ውድም በአኩስምና በአከባቢዋ የነበሩ 
ታቦታትንና ንዋያተቅዱሳትን በመያዝ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወደ ዝዋይ መጣ፡፡


Saturday 21 July 2012

ቤተክርስቲያን እንዴት ተመሠረተች ?

ዲያቆን መልአኩ እዘዘው








ስለ ክርስትና ሃይማኖት ስለ ቤተክርስቲያን በምንናገርበት ጊዜ ሁሉ ትዝ የሚለንና የምናስተውለው የመጀመሪያው ሰው የአዳም ሁኔታ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን እግዚአብሔር የሁላችንን አባት አዳምን በአርአያውና በመልኩ ከፈጠረው በኋላ ባረከው፡፡

Wednesday 11 July 2012

ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ጳውሎስ

ዲያቆን ታደሰ ወርቁ
እነዚህ ሁለት ቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስት ቤተክርስቲያናችን አዕማድ ናቸው፡፡ በመሠረትነት በአጸኗት ቤተክርስቲያን ያላቸው የክብር ሥፍራ ላቅ ያለ ነው፡፡ ይህ የሆነው እንዲሁ አይደለም፡፡ ለቤተክርስቲያንና በቤተክርስቲያን የፈጸሙት አገልግሎት በዚህም የተቀበሉት ሰማዕትነት ነው፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትም ይህን መልካም የሆነውን ታሪካቸውን ለእኛ አርአያነት በሚሆን መልኩ ከትበውልናል፡፡ እኛም ለአርአርያነት በሚሆን መልኩ የእነዚህን ደጋግ ሁለት ቅዱሳን አባቶች ታሪክ፣ ዕውቀትና መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን ከዚህ በመቀጠል አቅርበናል፡፡
1. ሁለቱ ሐዋርያት ሲጠሩ የነበሩበት ሕይወት
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተ ሳይዳ ሲወለድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ ደግሞ በጠርሴስ ከተማ ተወለደ፡፡