በዊኒፔግ - ካናዳ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ወቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ዜናዎች ብሎግ Blog of the Ethiopian Orthodox Tewahedo St Mary's and St Gabriel's Church in the City of Winnipeg, Manitoba, Canada
Wednesday, 30 November 2011
Sunday, 27 November 2011
«ጾምን ቀድሱ» /ኢዮ.2-15/
ጾም
የሰውን ልጆች የሚወደውና ስለ እነርሱም ብሎ በገነት ያሉትን ዛፎች ሁሉ የፈጠረው እግዚአብሔር በገነት ካሉት ዛፎች መካከል አንዲቱን እንዳይበላ አዳምን አዘዘው፡፡ ይኽ አዳምን ለመጫን፣ ኃይሉን በእርሱ ላይ ለማሳየት ሳይሆን ሰው በመጾም /ባለመብላት/ እና በመታዘዝ ለሚወደው አምላኩ ፍቅሩን ይገልጽ ዘንድ ነው፡፡
ከአዳም ድቀት በኋላም በየዘመናቱ የተነሡ መንፈሳውያን ሰዎች እና ሕዝቦች በየግላቸው እንዲሁም በአንድነት /በጋራ/ ሲጾሙ፣ በጾማቸውም ሲጠቀሙ ኖረዋል /ሕዝበ እስራኤል ሙሴ፣ ኤልያስ፣ የነነዌ ሰዎች. . ./፡፡
ጌታችንም፣ በእደ ዮሐንስ ከተጠመቀ በኋላ፤ የማስተማር አገልግሎቱን ከመጀመሩ በፊት ጾሟል፡፡
ከዚህ ክርስቲያናዊ ትውፊት በመነሣትም ሐዋርያትና ደቀመዛሙርቱም እንዲሁ አገልግሎታቸውን ከመጀመራቸው በፊትና በአገልግሎታቸው ወቅት ይጾሙ ነበር፡፡ Wednesday, 23 November 2011
ጾመ ነቢያት
እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ
ዘመኑ ጾመ ነቢያት የተባለበት ምክንያት ነቢያት የተናገሩት ትንቢት
ስለ ተፈጸመበት እንዲሁም በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምሥጢር
ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ የረቀቀው ገዝፎ እየተመለከቱ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ስለ ጾሙ ስለ ጸለዩ ነው፡፡
ነቢያት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ፣ ወደ ግብፅ ስለ መሰደድ፣
በባሕረ ዮርዳኖስ ስለመጠመቅ፣ በትምህርተ ወንጌል ጨለማውን
ዓለም ስለ ማብራቱ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ
ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ትንሣኤው፣ ስለ ዕርገቱና
ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፤
ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት
ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን
ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው «አንሥእ ኃይለከ፣
ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሳ እጅህንም ላክ» እያሉ ጮኹ፡፡
በጾምና በጸሎት ተወስነውም ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡
ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ
በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ
ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡
Sunday, 20 November 2011
Zemarit Alem Zegeye
Our sister Zemarit Alem Zegeye - beloved daughter of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, whose life was dedicated to the service of our Lord, Savior and God Jesus Christ has departed to join the Saints in Heaven. Her body has been laid to rest in her native Kombolcha town - near the City of Harar. A memorial service has been conducted at her Debre Genet St Mary's and St Gabriel's church in Winnipeg, Canada today - November 20, 2011. Alem has upheld her purity and was living in Holy Communion. She was patient and soft spoken but fiercely loyal to her Orthodox Tewahedo Christian religion. She served the church with dedication, vigour and energy. We will all miss you dear Alem! You have been loyal to the Orthodox Tewahedo faith to your last breath. Your life is a model for us! We all love you. We pray that the Lord give us the strength to stand firm like you did in the one and true faith - Tewahedo - till the last second of our life. We pray that the Lord give us the strength to abhor sin and live in sanctity and Holy Communion like you did.
Winnipeg loves you dear Alem!
Debre Genet - your beloved Church will always remember you and honour you!
Rest in peace Alem dear!!
Saturday, 19 November 2011
Thursday, 17 November 2011
Monday, 14 November 2011
Sunday, 6 November 2011
Tuesday, 1 November 2011
ዲ/ን ዳንኤል ክብረት "ትኩስ ወይም በራድ ስላልኾንኽ ልተፋህ ነው" ክፍል አንድ D.N Daniel Kibret
ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
"ትኩስ ወይም በራድ ስላልኾንኽ ልተፋህ ነው"
ክፍል አንድ
"ትኩስ ወይም በራድ ስላልኾንኽ ልተፋህ ነው"
ክፍል አንድ
ዲ/ን ዳንኤል ክብረት "ትኩስ ወይም በራድ ስላልኾንኽ ልተፋህ ነው" ክፍል ሁለት D.N Daniel Kibret
ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
"ትኩስ ወይም በራድ ስላልኾንኽ ልተፋህ ነው"
ክፍል ሁለት
"ትኩስ ወይም በራድ ስላልኾንኽ ልተፋህ ነው"
ክፍል ሁለት
Subscribe to:
Posts (Atom)