Wednesday, 14 December 2011

Tuesday, 13 December 2011

በአታ ለማርያም


በአታ ለማርያም

ታኅሣሥ 3/2004 ዓ.ም
በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

Mariam1ሰይጣን በእባብ አካል ተሰውሮ ሔዋንን፤ በእርሱዋም አዳምን በማሳት በእነርሱ ላይ ሞት እንዲሠለጥንባቸው ስላደረገ “በአንተና በሴቲቱ መካከል፣ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደረጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፤ አንተም ሰኮናውን ትነድፋለህ” በማለት የፍቅር አምላክ እግዚአብሔር ፈረደበት፡፡ “በአንተ” የተባለው ሰይጣን ሲሆን፣ “በሴቲቱ” የተባለችው ቅድስት ድንግል ማርያም ናት (ገላ.4፡4)፣ “በዘርህ” ሲል የዲያብሎስ የግብር ልጆችን ሲሆን(ዮሐ.8፡49)፣ “በዘርዋ” የተባለው ክርስቶስ ነው(ገላ.3፡16)፡፡ ትርጉሙ እንዲህ አንደሆነም ወንጌላዊው ዮሐንስ “ዘንዶው በሴቲቱ ላይ ተቆጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ የጠበቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ በባሕርም አሸዋ ላይ ቆመ”አለን፡፡(ራእ.12፡17) እባብ የተባለው ሰይጣን ስለመሆኑም “ዓለሙን ሁሉ የሚያስተው ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ”(ራእ.12፡9) ብሎ ጻፈልን፡፡

Saturday, 10 December 2011

በዊኒፔግ ካናዳ የ2004 ኅዳር ጽዮን በዓል ፎቶዎች Hidar Tsion 2011 Festival in Winnipeg, CANADA - photos

‎"ጽዮንን ክበቡአት፥ 
በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ 
ግንቦችዋንም ቍጠሩ፤ 
በብርታትዋ ልባችሁን አኑሩ፤ 
አዳራሽዋን አስቡ፤ 
ለሚመጣው ትውልድ ትነግሩ ዘንድ።" 
መዝሙር 48: 12-13

በዊኒፔግ ካናዳ የ2004 ኅዳር ጽዮን በዓል ፎቶዎችን ለመመልከት ይህንን ይጫኑ!! Click here to view celebration of Hidar Tsion 2011 in Winnipeg, Canada

Tuesday, 6 December 2011

የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን በዋሻ ውስጥ ተገኘ


ምንጭ አንድ አድርገን ብሎግ

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የሰማነው እግዚአብሔር አሁንም  አብሮን እንዳለ 

በምህረቱም እየጎበኝን እያለ መሆኑን ነው፤ በጠላት ወረራ ጊዜ የተቀበረውን 
የቅዱስ ገብርኤልን ቤተክርስትያ በማውጣት አሳይቶናል ፡፡
እግዚአብሔር ይመስገን:: እግዚአብሔር አልተወንም ፤ 
አይተወንም የሚያስብል ተዓምር ነው የተደረገው፡፡ 

Thursday, 1 December 2011

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ታቦተ ጽዮን


ኅዳር 20/2004 ዓ.ም
ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ካወጣቸው በኋላ የአምልኮ ሥርዐታትን ይፈጽሙበት ዘንድ የምስክሩን ድንኳን፣ የቃል ኪዳኗ ታቦትንና ለአምልኮ ሥርዐቱ ማከናወኛ የሚያገለግሉ ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳትን እንዲሠሩ በሙሴ በኩል ታዘው ነበር፡፡ ከቃል 3p-03ኪዳኗ ታቦት ውስጥም በእግዚአብሔር ጣት ዐሥርቱ ትእዛዛት የተጻፉበት የሕጉ ጽላት፣ አርባ ዓመት ሙሉ እስራኤላውያን በሲና ምድረ በዳ የተመገቡትን መና የያዘች መሶበ-ወርቅ፣ አሮን ለክህነት አገልግሎት ስለመመረጡ ምስክር የሆነችው ለምልማና ፍሬ አፍርታ የተገኘችው የአሮን በትር ይገኙባታል፡፡(ዕብ.9፡4)